Sunday, February 17, 2013

አይሁዳዊያን መጻሕፍት





              አይሁዳዊያን  መጻሕፍት

    አይሁዳዊያን በትውፊት ከቀደሙ አባቶቻቸው የወረሷቸው ሁለት አይነት ሃይማኖታዊ መጻሕፍት አሏቸው። የመጀመሪያዎቹ በጽሁፍ ተዘጋጅተው ከቀድሞ አባቶቻቸው የተረከቡት መጻሕፍት ሲሆኑ በዕብራይስጥ "ቶራ ሼ-በክታቭ" ይባላሉ ለምሳሌ ያህል አምስቱ የሙሴ መጽሐፍት ናቸው። ሁለተኞቹ ከቀድሞ አባቶች በትውፊት በቃል የተረከቡት መጻሕፍት ናቸው በዕብራይስጥ "ቶራ ሼ-በአልፔ" ይባላሉ ለምሳሌ  ያህልም የ"ታልሙድ" እና የ"ሚድራሽ" መጻሕፍት ናቸው።

ታልሙድ (תַּלְמוד)

   በአምስቱ የሙሴ መጽሐፍት የተጻፉ አድርግና አታድርግ የሚሉትን ትእዛዝ የሚተሮግምና የሚያብራራ  የቶራ ሼ-በአልፔ መጽሐፍ ሲሆን ይህ መጽሐፍ የአይሁድ ታላላቅ ራባዮች (ራባናት- የአይሁድ መምህራን) ለተማሪዎቻቸው በተለያየ ጊዜ የኦሪት ህግጋትን በተመለከተ ያስተማሮቸው ትምህርቶች የያዘ ነው። ይህም ትምህርት ከትውልድ ትውልድ በቃል ሲወርድ-ሲዋረድ ቆይቶ ራባዮች በቃል የሰሟቸውን  "በቃል ያለ ይረሳል በጽሑፍ ያለ ይወረሳል" እንደሚባለው እንዳይረሳ እነዚህን ትውፊታዊ ትምህርቶች ጻፎቸው። እነዚህንም በሁለተኛው መቶ ክፍለ ዘመን በሊቀ ራባናት ይሁዳ  ሃነሲ ተሰብስቦ ተጠረዘ ። ራብ ይሁዳ እነዚህን የታልሙድ ጥራዛት ሲያዘጋጃቸው በስድስት ክፍሎች ("ሺሻ ሴዴሪም"  (six orders)) ከፋፍሎ ነው ። እነዚህም የታልሙድ ስብስቦች ሚሽናህ  ተብለው ይጠራሉ። 




ሚሽናህ (משנה)

    ሚሽናህ የሚለው ስያሜ ሻናህ (ከለሰ ፣ ደገመ) ከሚለው የዕብራይስጥ ግስ የተገኘ ቃል ሲሆን ፤ ሚሽናህ ማለት መከለስ መድገም ማለት ነው። ራባይ ይሁዳ  ሃነሲ በ220 ዓም በቃል የነበሩት የኦሪ ትምህትቶችን አሰባስቦ ለመጀመሪያ ጊዜ በጥራዝ አዘጋጅቶታል። ሚሽናህ የታልሙድ ክፍል ሲሆን ፤ በእያንዳንዱ የሚሽናህ ትርጓሜ ትምህርቶች ላይ ራባናት ተከራክረውና ተወያይተው የወሰኑት የመጨረሻ የመደምደምያ ትምህርታቸውን አስፍረዋል ፤ ይህም በዕብራይስጥ "ግማራ" ይባላል።


ታናህ የአይሁዳዊያን መጽሐፍ ቅዱስ ሲሆን በውስጡ ሶስት የቅዱሳት መጻሕፍት ስብስብ ይዟል፤ እነርሱም ቶራ፣ንቪኢም እና ክቱቪም ናቸው

ቶራ (תּוֹרָה)  
    ቶራ የቃሉ ትርጓሜ መራ ፣አዘዘ እንደማለት ነው። መጽሐፈ ቶራ የአይሁዳዊያን ታላቅ መጽሐፍ ሲሆኑ፤ የታናህ የመጀመሪያው ክፍልም ነው። መጽሐፈ ቶራ አምስቱ የሙሴ መጻሕፍትን አጠቃሎ የያዘ ነው ። አምስቱ የሙሴ መጻሕፍት የሚባሉትም ከዚህ በታች የተዘረዘሩት ናቸው ፦
א.       ኦሪት ዘፍጥረት  (በዕብራይስጥ ቋንቋ  "በሬሼት בראשית " ተብሎ ይጠራል )
ב.       ኦሪት ዘጸአት  (በዕብራይስጥ ቋንቋ  "ሼሞት שמות "  ተብሎ ይጠራል  )
ג.        ኦሪት ዘኁልቁ (በዕብራይስጥ ቋንቋ  "ቨዪክራ ויקרא " ተብሎ ይጠራል  )
ד.        ኦሪት ዘሌዋውያን (በዕብራይስጥ ቋንቋ  "በሚድባር במדבר " ተብሎ ይጠራል  )
ה.       ኦሪት ዘዳግም  (በዕብራይስጥ ቋንቋ  "ዴቫሪም דברים "ተብሎ ይጠራል )
ቪኢም (נְבִיאִים) 
   ንቪኢም ማለት የቃሉ ትርጉም ነብያት ማለት ነው። መጽሐፈ ንቪኢም ሁለተኛው የታናህ ወይም የአይሁድ መጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ሲሆን የነብያት ትንቢታቸው የሰፈረበት መጽሐፍ ነው። መጽሐፈ ንቪኢም ሁለት ክፍሎች ሲኖሩት መጽሐፈ ኢያሱ፣ መጽሐፈ መሳፍንት፣ መጽሐፈ ሳሙኤልና መጽሐፈ ነገስት ባንድላይ "ንቪኢም ርሾኒም" (የመጀመሪያውያዎቹ ነብያት) መጽሐፍት ሲባሉ፤ እንዲሁም ትንቢተ ኢሳያስ፣ትንቢተ ኤርምያስ፣ ትንቢተ ሕዝቅኤልና አስራ ሁለቱ ንዑሳን ነብያት "ንቪኢም አሀሮኒም" (የመጨረሻዎቹ ነብያት) የጻፎቸው መጽሐፍት ናቸው። መጽሐፈ ንቪኢም ተብለው የሚጠሩት ባጠቃላይ  የሚከተሉት ናቸው ፦
1.    መጽሐፈ ኢያሱ
2.   መጽሐፈ መሳፍንት
3.   መጽሐፈ ሳሙኤል
4.   መጽሐፈ ነገሥት
5.   መጽሐፈ መክብብ  
6.   ትንቢተ ኢሳያስ
7.   ትንቢተ ኤርምያስ
8.   ትንቢተ ሕዝቅኤል
9.   ትንቢተ ሆሴዕ
10.  ትንቢተ ኢዩኤል
11.   ትንቢተ አሞጽ
12.  ትንቢተ አብድዩ
13.  ትንቢተ ዮናስ
14.  ትንቢተ ሚክያስ
15.  ትንቢተ ናሆም
16. ትንቢተ ዕንባቆም
17.  ትንቢተ ሶፎንያስ
18.  ንቢተ ሐጌ
19.  ትንቢተ ዘካርያስ
20. ትንቢተ ሚልክያስ ቸው።


ክቱቪም (כְּתוּבִים)
    ክቱቪም ማለት መልእክታት ወይም ጽሑፎች ማለት ነው። ክቱቪም ሶስተኛውና የመጨረሻው የአይሁድ መጽሐፍ ቅዱስ (የታናህ) ክፍል ሲሆን ይህን መጽሐፍ የተለያዩ የእግዚአብሔር ሰዎች የከተቧቸው መጽሐፍት ናቸው ። የክቱቪም መጻሕፍት የሚከተሉት ናቸው ፦
§  መጽሐፈ ኢዮብ
§  መዝሙረ ዳዊት
§  መጽሐፈ ምሳሌ
§  መኃልዬ መኃልይ ዘሰለሞን
§  መጽሐፈ ሩት
§  ሰቆቃው ኤርምያስ
§  መጽሐፈ መክብብ
§  መጽሐፈ አስቴር
§  ትንቢተ ዳንኤል
§  መጽሐፈ ዕዝራ
§  መጽሐፈ ነህምያ
§  መጽሐፈ ዜና ናቸው።



















No comments:

Post a Comment